የጉመር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ
አቶ አዲሱ ሰማኒ
የጉመር ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ
ራዕይ

በ2023 ዓ/ም በወረዳው ፍትሀዊነቱና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርትና ስልጠና በማዳረስ በዕውቀት፣ በክህሎትና በአመለካከት የተስተካከለና ለልማት፣ ለፍትሕ፣ ለሰላምና ለዲሞክራሲ ግንባታ በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ የላቀ ሚና የሚጫወትና በገበያ ላይ ብቁ ተወዳዳሪ የሆነ ትውልድ ተፈጥሮ ማየት

ተልዕኮ

በወረዳው የተፋጠነና ቀጣይነት ያለው ዕድገትና ልማት እንዲመጣና ዴሞክራሲያዊ ባሕል እንዲዳብር ፍትሃዊነቱና ተገቢነቱ የተረጋገጠና ጥራቱ የተጠበቀ የትምህርት አገልግሎት በማዳረስ ክህሎቱና እውቀቱ ያደገ እንዲሁም አመለካከቱ የተስተካከለ ትውልድ ለመፍጠርመደበኛና መደበኛ ያልሆነ የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራሞችን በመጠቀም፣ ትምህርትና ስልጠናን በቴክኖሎጂ እንዲሁም በጥናትና ምርምር በማስደገፍ፣ ህብረተሰቡን በባለቤትነት በማሳተፍ፣ አጋር ድርጅቶችን በማስተባበርና የተገኘውን ሃብት በአግባቡ በመጠቀም ትምህርትን ለዜጎች ሁለ ተደራሽ ማድረግ ነዉ፡፡

እሴቶች
  • ለሙያዊ ሥነምግባር መገዛት
  • ለጊዜ ዋጋ መስጠት
  • በሥራክቡርነት ማመን
  • ተገልጋዮችን በቅንነት ማገልገል
  • ሙስናን መጠየፍ
  • የለውጥ ሀዋሪያ መሆን
  • ሁሌም መማር