የጉመር ወረዳ ሚሊሻ ፅ/ቤት

ራዕይ

የዜጐች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች፣ የህግ የበላይነትና የመልካም አስተዳደር፣ የህዝቡ ሰላም ፀጥታና ደህንነት የተረጋገጠበት ወረዳ ተፈጥሮ እና ለዚሁም ጉልህ ድርሻ የሚያበረክት ተቋም ሆኖ ማየት

ተልዕኮ

አሰራሮችንና አደረጃጀቶችን ዘመናዊ በማድረግ ጠንካራ የፀጥታ መረጃ ስርዓት በመፍጠር፣ በህብረተሰቡ ንቁ ተሣትፎ የሚታገዝና ብቃት ያለው የፀጥታ ኃይል በማፍራት ግጭቶችን በሃይማኖት ወይም በእምነት ሽፋን የሚፈፀም የአክራሪነትና የጽንፈኝነት አመለካከትን በብቃት በመለየትና በመከላከል የወረዳዉን ፀጥታ፣፡ ሰላምና ደህንነት መጠበቅና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በማስከበር የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ፡፡

እሴት

እሴቶች የሴክተሩ ሰራተኞች የስራ አመራሩ የሚመሩባቸውና ወደ ፊትም በጋራ ሊከተሏቸው የሚገቡ የግልና የተቋም የአሰራር ፍልስፍናዎች ሲሆኑ ተቋሙ፡-

  • ለህገ-መንግስቱ ታማኝ መሆን
  • የህብረተሰቡን ተሣትፎ ማረጋገጥ
  • ሀብትን በአግባቡና በቁጠባ መጠቀም
  • የህዝብ አገልጋይነት
  • ብዝሃንነትን መቀበልና መክበር
  • ፍትሃዊነትና ሰብአዊነትን መላበስ
  • ራስን ማብቃት አዳዲስ አሰራሮችን ማወቅና መጠቀም
  • ሙያዊ ስነ-መግባር መላበስ
  • ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ትኩረት መስጠት እና ኃላፊነትን መወጣት